ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በዋናው ግቢ የአማን ካምፓስን ጨምሮ 1,290 ተማሪዎችን በደማቅ ስነ ስርዓት ለ16ኛ ጊዜ አስመርቋል።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ሚቴዩ ፣ሰኔ 27/2016
ዩኒቨርስቲው በዋናዉ ግቢ ከአራት ኮሌጆችና ከአንድ ትምህርት ቤት ቁጥራቸው 1,111 የቅድመ ምረቃ እንዲሁም በልዩ ልዩ የትምህርት መስኮች የተማሩ 179 የድህረ ምረቃ ፕሮግራም በድምሩ 1,290 ተማሪዎችን በዛሬው እለት አስመርቋል።
![](https://www.mtu.edu.et/wp-content/uploads/2024/07/image-4.png)
![](https://www.mtu.edu.et/wp-content/uploads/2024/07/image-5.png)
![](https://www.mtu.edu.et/wp-content/uploads/2024/07/image-6.png)
በምረቃ ስነስርዓቱ ላይ ክቡር አምባሳደር አል ቡሲራ ባስኑር በኢትዮጵያ ፤ ጅቡቲ ፤ እና የአፍሪካ ሕብረት የኢንዶኔዥያ ሪፐብሊክ አምባሳደር ፤ የእለቱ ልዩ የክብር እንግዳ ፤ ክቡር አቶ ጸጋዬ ማሞ የደቡብ ምዕራብ ህዝቦች ክልላዊ መንግስት የመንግስት ዋና ተጠሪ ፤ ክቡር አቶ ሐብታሙ ካፍትን የቤንች ሸኮ ዞን አስዳዳሪና የዩኒቨርስቲው ቦርድ አባል ፤ ክቡር ዶክተር ጴጥሮስ ወ/ጊዮርጊስ የቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ፤ ክቡር አቶ ግሩም ተማም የሚዛን አማን ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ፤ ተጋባዥ እንግዶች ፤ የሃይማኖት አባቶችና የተመራቂ ቤተሰቦች ተገኝተዋል።